previous arrow
next arrow
Upcoming event, 2017/2025 Graduation.
Slider
Students
Staff
7
Campuses
10
8 Colleges and 3 Institutes
Programs
Partnerships

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ኮሌጅ በሳይንሳዊ የወረቀት አፃፃፍ ክህሎት ላይ በዋናው ግቢ በ03-07-2013 ዓ.ም ስልጠና በሰጠበት ወቅት በቦታው የተገኙት የትምህርት ኮሌጁ የትምህርት እና ቴክኖሎጂ ስርፀት ተባባሪ ዲን ዶ/ር ማርቆስ መኩሪያ

በንግግራቸው የትምህርት ኮሌጁ ወደ ኮሌጅ ደረጃ ከማደጉ በፊት ትምህርት እና ስልጠና ይባል እንደነበረ ገልፀው ወደ ኮሌጅ ካደገበት ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ በመማር ማስተማሩ፣ በምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም በማህበረሰብ አገልግሎት ሥራዎች ላይ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።

ተባባሪ ዲኑ አክለው ሲናገሩ ኮሌጁ የምርምር ሥራውን ሳይንሳዊና ዓለም አቀፋዊ ለማድረግ በማለም ይህ ስልጠና እንደተዘጋጀ አብራርተው በዚህ ስልጠና ለይ ተሳታፊ የሆኑ መምህራንና ተመራማሪዎች ምርምሮቻቸውን ሳይንሳዊ በማድረግ ረገድ በቂ ክህሎት እንደሚያገኙና በዚህም በርካታ የምርምር ሥራዎችን በውጤታማነት እንደሚያጠናቅቁ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።

የትምህርት ኮሌጅ ዕቅድና ሥራ አመራር አካቶ ዘርፍ ተባባሪ ዲን የሆኑት ዶ/ር አንተነህ ዋሲሁን በበኩላቸው ተሳታፊ ሰልጣኞች በኮሌጁ ውስጥ ከሚገኙ አራት ት/ክፍሎች የተወጣጡ መሆኑን የገለጹ ሲሆን ስልጠናው የምርምር ሥራዎቻቸውን በዓለም አቀፍ ደረጃ በማሳተሙ ላይ የሚታየውን ክፍተት ይሞላል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል፡፡ ስልጠናው በዚህ ብቻ ሳይገደብ ተመሳሳይና ሰፋ ያለ ስልጠና ለሁሉም መምህራን የሚሰጥበት ሁኔታ ቢመቻች ተመራማሪዎች የተሻለ እውቀት የሚያገኙ ሲሆን ሃገሪቱም በዚሁ ዘርፍ ተጠቃሚ ትሆናለች ብለዋል።

በመጨረሻም በዕለቱ ስልጠናውን የሰጡት የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ኃላፊ ፕ/ር ተስፋዬ ሰመላ ሲናገሩ በስልጠናው የተሳተፉ መምህራኖች ከስልጠናው የሚያገኙአቸውን ክህሎቶች በአግባቡ በመጠቀም በሚያከናውኑአቸው ምርምሮች ላይ የተሻለ ውጤታማነትን ሊያመጡ እንደሚገባ ሀሳባቸውን ሰጥተዋል።

 Ato Tiratu Beyene Biltu
Ato Tiratu Beyene Biltu
Addis Ababa City Administration
I graduated from HU with a BSc in Applied Chemistry in 2005GC.
Dr Abeba Yeshitla Demessa
Dr Abeba Yeshitla Demessa
Assosa University
I am one of the 2006 GC graduates of HU from the department of Biology.
Anteneh Gizaw Beyene
Anteneh Gizaw Beyene
Ethiopian Press Agency
I am one of the 2005 GC graduate of HU from the department of Foreign Language and Literature/ DFLL/.

Contact Us

Office of External Relations & Communications 
Phone:  +251 46 220 5168
International Relations
Public Relations 

Touch Us

Registrar Contact 

Registrar Directorate 
Phone: 0462200229
Email: registrar@hu.edu.et