በሀዋሳ ዩ. ጤ ሳ. ኮ. ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በተጋበዙ መምህራን የተግባር ምዘና ለተመራቂ ተማሪዎች በመከናወን ላይ ይገኛል

በሀዋሳ ዩ. ጤ ሳ. ኮ. ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በተጋበዙ  መምህራን የተግባር ምዘና ለተመራቂ ተማሪዎች በመከናወን ላይ ይገኛል።

የኮሌጁ ስኪል ላቦራቶሪ ማናጀር የሆኑት ረ/ፕ ኤፍሬም ጌጃ እንደገለፁት ከመስከረም 12, 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ለተከታታይ ሁለት ቀናት ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች በመጡ ልምድ ባላቸው መምህራን የተግባር ምዘና /OSPE external exam/ ለነርሲንግ ትምህርት ቤት ተመራቂ ነርሲንግ ተማሪዎች በማከናወን ላይ ይገኛል። በተለይም በዩኒቨርሲቲያችን እንዲሁም በአገር አቀፍ ደረጃ የትምህርት ጥራት ላይ ትኩረት ሰጥተን መስራት ላይ ባለንበት በዚህ ወቅት ዩኒቨርሲቲው የራሱን መምህራን በመጠቀም ከሚደርገው የተግባር ምዘና ጎን ለጎን ተመርቀው ወደ ስራ ገበታቸው ከመመደባቸው በፊት ይህን ዓይነት ምዘና ማድረግ ተገቢ እና አስፈላጊም ጭምር መሆኑን ገልፀዋል።

Contact Us

Office of External Relations & Communications 
Phone:  +251 46 220 5168
International Relations
Public Relations 

Touch Us

Registrar Contact 

Registrar Directorate 
Phone: 0462200229
Email: registrar@hu.edu.et