ከኢኖቬሽንና ቴከኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከኢኖቬሽንና ቴከኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከኢኖቬሽንና ቴከኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር የምርምር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የኢኖቬሽን እና ስታርታፖችን የመደገፍ ብሎም ምቹ ስነ-ምህዳር ለመፍጠር የሚያስችሉ ስራዎች በትብብር ለማከናወን የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ግንቦት 16/2016 ዓ.ም ተፈራርሟል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ ከድሬዳዋ፣ ጅማ እና ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በተደረገው የጋራ መግባቢያ ስምምነት ፊርማ ስነስርዓት ላይ እንደገለፁት ስምምነቱን በኢኖቪዝ-ኬ ኢንኩቤሽን ማዕከል እና በዩኒቨርሲቲዎች ያሉ አቅሞችን አቀናጅቶ በመጠቀም በዘርፉ ውጤት ለማምጣት ያለመ መሆኑን አስረድተዋል።
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲን በመወከል ስምምነቱን የተፈራረሙት የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚደንት ዶ/ር ታፈሰ ማቲዮስ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው የፈጠራ፣ የምርምር እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎችን ለመስራት ያለውን ከፍተኛ ፍላጎትና እምቅ አቅም ጠቅሰው ይህን መሰል ቅንጅት መፈጠሩ እንደሀገር ያሉ አቅሞች እንዳይባክኑ ያደርጋል ብለዋል።

Contact Us

Office of External Relations & Communications 
Phone:  +251 46 220 5168
International Relations
Public Relations 

Touch Us

Registrar Contact 

Registrar Directorate 
Phone: 0462200229
Email: registrar@hu.edu.et